Tuesday, September 10, 2013

ባሕረ ሐሳብ

እንኳን ለ፳፻፮ /2006/ ዓመተ ምህረት ዘመነ
ማርቆስ በሰላም በጤና አደረስዎ!

Ø  ባሕረ ሐሳብ ከሁለት የግዕዝ ላት የተገኘ ሲሆን
ባሕር  =  ዘመን
ሀሳብ  =  ቁጥር ማለት ነው። /ዝርዝሩን ከብሎጉ ይመልከቱ/ 

ባሕረ ሐሳብ ማን ደረሰው ?
Ø  የእስክንድርያ 12 ሊቀ ጳጳስ (ፓትርያርክ) የነበረው ቅዱስ ሜጥሮስ
180 – 222 . ድረስ 42 ዓመት ሊቀ ጳጳስ ነበር። ሊቀጳጳስ ከመሆኑ በፊት መስተገብረ ምድር (ገበሬ) ነበር። አርቆ በአጭር ታጥቆ የሚሰራ ትጉህ ገበሬ ነበር። ከልዕልተ ወይን (የቤተክርስቲያን ለቃውንት የሚጠሯት ስም) ጋር አጋብተዋቸው ነበር።
የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ ዩልዩስ (ዩልያኖስ) ሹሞታል።  /ሙሉ ታሪኩን ብሎጉን ይጎብኙ/

ባሕረ ሐሳብ በመጽሐፍት ቤት
Ø  ቤተ ክርስቲያን አራት ጉባዔ ቤቶች አሏት
·         ብሉይ ኪዳን
·         ሐዲስ ኪዳን
·         መጽሐፈ መነኮሳት (ማር ይስሐቅ፣ ፈልክዲዳዩስ)
·         ሊቃውንት (ሃይማኖተ አበው)
·         አምስተኛ ጉባዔ  ተደርጐ በሁለት መንገድ ይሰጣል። አቡከክር (አቡካኻር) ባሕረ ሀሳብ ተብሎ
Ø  አቡካኻር (ወልደ አቤል ሄሬም) የተባለ መነኩሴ ሲሆን ባሕረ ሐሳብን ጨምሮ ሌሎች የሥነ ጸሐይ፣ ጨረቃና ከዋክብት ሊቅ ነው። ባሕረ ሀሳብም አብሮ ተገልጾለታል።